Friday, May 17, 2013

የማቅ ታማኝ አገልጋይ አባ ኅሩይ ወንድ ይፍራው ከሥራ አስኪያጅነታቸው ታገዱ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለ4 ከተከፈለ በኋላ የምዕራብ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት አባ ሕሩይ ወንድይፍራው ከስራ አስኪያጅነታቸው መታገዳቸውን የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ለመነኩሴው በጻፈው የእግድ ደብዳቤ አስታወቀ፡፡ በደብዳቤው እንደ ተገለጸው ለአባ ሕሩይ መታገድ ምክንያቶቹ የተመደበቡበትን የሥራ ሃላፊነት በአግባቡ አለመወጣትና ከሊቀ ጳጳሱ መመሪያ ሳይቀበሉና ትእዛዝ ሳይሰጥ ለሙስናና ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ የሰራተኛ ቅጥር፣ የደመወዝ ጭማሪና የሰራተኛ ዝውውር ማድረግን እንደሚመለከት ለማወቅ ተችሏል፡፡ እነዚህን ህገወጥና ከፍተኛ ጉቦ የሚበላባቸውን ተግባራት ሲፈጽሙ መቆየታቸው ስለተደረሰበት ከስህተታቸው እንዲታረሙ በየደረጃው ከቃል እስከ ጽሑፍ ምክርና ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም አባ ሕሩይ ማስጠንቀቂያውን ከቁብ ሳይቆጥሩ በተበላሸ አሰራራቸው በመቀጠላቸው ምክንያት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁእ አቡነ ሕዝቅኤል ከሥራ አስኪያጅነት እንዳገዷቸው ደብዳቤው ያመለክታል፡፡

Tuesday, May 14, 2013

ልደታ በአታ እና ኪዳነ ምሕረት ማናት?

ይህ ጥያቄ ላልተማሩ ካህናትና ምእመናን ቢቀርብ “እመቤታችን ናታ!” እንደሚሉ አያጠራጥርም፡፡ ምክንያቱም “ልደታ” “በአታ” እና “ኪዳነ ምሕረት” በሚሉ ስሞች ጽላት ተቀርጾአል፤ ቤተክርስቲያን ታንጿል፤ መጽሐፍም ተጽፎ ሊሆን ይችላል፡፡ ሊቃውንቱና የተማሩ ምእመናን ግን እነዚህ ስያሜዎች በሂደት የማርያም መጠሪያ ስሞች ተደርገው ተወሰዱ እንጂ ልዩ ልዩ ተግባራት የተከናወኑባቸውን ዕለታት ለማሰብ የተሰጡ ስያሜዎች እንደሆኑ ሊነግሩን ይችላሉ፡፡ አክለን “ቤተክርስቲያንን የሚመሯት ሊቃውንቱ ናቸው ወይስ ያልተማሩና ትምህርተ ሃይማኖት የሌላቸው ካህናትና ደባትራን?” ብለን ብንጠይቅ ደግሞ ምላሹና እውነታው ለየቅል ይሆንብናል፡፡ ምክንያቱም ሊቃውንቱ ናቸው ካልን ማርያም የተወለደችበትን ቀን ለማሰብ ቀን መለየታቸው ልክ ባይሆንም ልክ ይሁን እንበልና ለዚህ መታሰቢያነት በተለየው ቀን ስም ጽላት መቅረጽንና ቤተክርስቲያን ማነጽን ግን ምን አመጣው? የሚል ጥያቄ ያስከትላል፡፡ ምክንያቱም ዕለቱ ከመታሰብ አልፎ በሴት ስም ተሰይሞ ወደመመለክ እየተሸጋገረ ነውና፡፡ ስለዚህ ሊቃውንቱ ይህን ሊያደርጉ እንደማይችሉ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ካደረጉ ግን ሊቃውንት የሚል የሙያ ስም ሊሰጣቸው አይገባም፡፡

Wednesday, May 8, 2013

የግንቦት 15ቱ ውግዘት መነሻ፣ ሂደት፣ ፍጻሜና ቀጣዩ ሲገመገም

ክፍል 14

«የእውነት ቃል አገልግሎት» ላይ የግንቦቱ (ግንቦት 15/2004 ዓ/ም) ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤው ያሰፈራቸውና «ኑፋቄ» ብሎ ካቀረባቸው ነጥቦች መካከል ቀጣዮቹን ነጥቦች መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርገን ኑፋቄ የተባሉት ነጥቦች ኑፋቄ መሆን አለመሆናቸውን እንመረምራለን።

 

«ሀ. ብቃት ያለውን አማላጅነት ትቶ እንደኛው ድካምን የሚለብሱና ለእነርሱ ለራሳቸው የክርስቶስ አማላጅነት የሚያስፈልጋቸውን አማላጅ ማድረግ ወይም በክርስቶስ ላይ ተጨማሪ አማላጅ አድርጎ ማዳበል ትልቅ ውደቀት ነው» በማለት ክርስቶስን አማላጅ አድርጎ የቅዱሳንን አማላጅነት ውድቀት በማለት ተሳድቧል።  መጽሐፈ ሰዓታት በመቅደሱ ሚዛን - ገጽ 64»

ስለአማላጅነት መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረውና በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሚታመነው የአማላጅነት ትምህርት ፈጽሞ አይገናኝም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱሳን በሕይወተ ስጋ ሳሉ ምልጃ ሲያቀርቡ እናነባለን፡፡ ካንቀላፉ በኋላ ግን ምልጃ ያቀረቡበት ሁኔታ የለም፡፡ ካንቀላፉ ቅዱሳን ጋር ሕያዋን ቅዱሳን የሚገናኙበት እድል ስለሌለም «ለምኑልን አማልዱን» ብለው ቢጮሁ ሰሚ የሌለው ጩኸት ነው የሚሆነው፡፡

Monday, May 6, 2013

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!



ትንሣኤን በትንሣኤ በሚል ርዕስ ዲያቆን አሸናፊ ብሎግ ላይ  የተጻፈውን ጽሑፍ እንዲያነቡ እንጋብዛለን።

Monday, April 29, 2013

የጻፍሁትን ጽፌአለሁ!

     ‘‘የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ’’    ዮሐ 19፡22
      ከንጉሥ ጲላጦስ  የተላከ
ጲላጦስ የይሁዳ አውራጃን ያስተዳድር የነበረ ሮማዊ ገዥ  ሲሆን   በስልጣን ዘመኑ ከተመለከታቸው ጉዳዮች እና ከአስቻላቸው ችሎቶች የኢየሱስ ጉዳይ የሚመስል እና ለመወሰን  የተቸገረበት ዘመን የለም።የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መሞት በዓለም   ከታዩት የፍርድ መጉደል ሁሉ የበለጠ ነው። አንድ ሰው በመስቀል ተስቅሎ  ከመሞቱ በፊት መገረፍ እንዳለበት የሮማውያን ህግ ይናገራል። ግርፉቱ  በጣም አደገኛ በመሆኑ  በግርፉቱ ብቻ  ብዙ ሰው ሞቷል ምክንያቱም መግረፊያው የሚሰራው ከቆዳ ሲሆን  በጫፉ ላይ ብረታ ብረት፡አጥንት ወይም ሹል ነገር ይቋጠርበታል። ወንጅለኛ የተባለው ሰው ሲገርፍ  እነዚያ ሁሉ ነገሮች በጀርባው ላይ ያርፉሉ፡ ከዚህ በኋላ ጉዳቱ የባሰ ሰለሆነ ሥጋው በማለቅ  አጥንቱ ከዚያም አልፎ ውሳጣዊ የሰውነት ክፍሎች  ይታያሉ።ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ  ሲገረፍ   ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ ደርሰውበታል። ጲላጦስ ብዙ ይተገረፈውን   ስጋው አልቆ አጥንቱ የታየውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚገባውን  ቅጣት ስለተቀበለ በነፃ ለማሰናበት በማለት በህዝቡ ፊት አቀረበው(ሉቃ 23፡16_22) አይሁድ ግን በደም የተሸፈነውን የኢየሱስን አካል በማየት ቅንጣት ያህል አላዘኑለትም፡ይልቁንም ምራቅ እየተፉ  በጥፊ ይመቱት ነበር(ማቴ 27፡27_31)። ኢየሱስ  እኛን ሰለሚወደን ይህን ሁሉ ታግሷል።ጲላጦስ ጌታ ኢየሱስን  ነፃ ለማድረግ  ብዙ መንገዶችን ሞክሯል ፦  እንዲለቁት ብሎ አስገርፎታል፡እናንተ ካልፈለጋችሁት  ግሪክ ሂዶ ያስተምር ብሎቸዋል፡ በየአመቱ የፉሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ  ኢየሱስን ከአደገኛው ወንበዴ ከበርባን ጋር ለምርጫ አቅርቧል። አይሁድ ግን ልባቸው በክፋት ስለ ተያዘ ኢየሱስ እንዳይፈታ በኃይል ይጮሁ ነበር፡የምትፈታው በርባንን ነው አሉ(ዮሐ18: 40)። ጩ ኸቱ ሁሉ  ወንበዴን ፈቶ ንጹሑን   ለመግደል ነው ። ጲላጦስ የ ሮምን  ሕግ ማስፈጸም ተሳነው ። ህጕ ወንጅል የሌለበትን አይቀጣምና። ጲላጦስ አንድ ንጹሕ መግደል ነው ያለበት? ወይስ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ውሸተኞችን መስማት?  በነገሩ ግራ ተግብቶ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ምን  ላድረገው (ማቴ 27፡22)  ሲላቸው  አይሁድም በአንድነት ስቀለው ስቀለው አሉ።  ጲላጦስ ግን አንዳች በደል አላገኘሁበትም   እናንተ ስቀሉት ሲላቸው እኛ ህግ አለን እንደ ህጋችን ሊሞት ይገባዋል ብለው  ወዲያዉኑ ኢየሱሰን ለመስቀል ወንጅል ያሉትን እራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ” ብሏል በማለት ነገሩን ከሮም ህግ  ወደ እግዚአብሔር ህግ ቀየሩት( ዮሐ198_11)   ጲላጦስ  ውሳኔ ግን ጌታን መልቀቅ ነበር ። የአይሁድ ካህናት ግን  እየሱስ  እንዳይለቀቅ ጲላጦስን በማስጠንቀቂያ   ብትፈታው የቄሳር  ወዳጅ  አይደለህም በማለት  ጉዳዩን  ከሃይማኖታዊ ወደ ፖለቲካዊ ይዘት ለወጡት።

አባ አብርሃም እና ማኅበረ ቅዱሳን በአሜሪካ ያለውን የሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ

                        ምንጭ፡- http://awdemihreet.blogspot.com/
 በማኅበረ ቅዱሳን አይዞህ ባይነት የአሜሪካውን ሃገረ ስብከት ጽ/ቤት ለብጹዕ አቡነ ፋኑኤል አላስረክብም ብለው የነበሩት አባ አብርሃም የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ፡፡ ይህ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፊርማ የወጣው እና አድራሻውን ለአባ አብርሃም ያደረገው ደብዳቤ እንዳስታወቀው አባ አብርሃም ሀገረ ስብከቱን በዝውውር ለቀው ከወጡ በኃላ የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አላስረክብም ማለታቸው ህገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡
አባ አብርሃም ቤተክርሰቲያን አንዲት መሆንዋን መረዳት ከብዷቸው እና እሳቸውን ለማዘዝ ሙሉ ስልጣን ያለውን ቅዱስ ሲኖዶስ ተጋፍተው ላለፉት ሁለት አመታት የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አላስረክብም በማለት በሀገረ ስብከቱ ውስጥ የሽፍታ ሠራዊት ማስፈራቸው አስገራሚ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ እኚህ ጉድ አያል ቅበት የሆኑት ጳጳስ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሳካው እሺ ብሎ በመታዘዝ መሆኑ ከዲቁና እስከ ጵጵስና ድረስ አለመረዳታቸው በብዙዎች ዘንድ የሚያስተዛዝብ ሆኗል፡፡

Sunday, April 28, 2013

ሆሳዕና በአርያም ለወልደ ዳዊት

እናንት መኳንንት በሮችን ክፈቱ የክብር ንጉሥ ይግባ
ሆሣዕና ከጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡ ጌታችን በተነገረው ትንቢት መሠረት በአህያ ላይ ተቀምጦ በክብር ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱ የሚታሰብበት በዓል ነው፡፡ በዓሉን ቤተክርስቲያን በሚታይ ትእምርት የምታከብረው ቢሆንም ትእምርቱ የሚወክለውን እውነት ግን ቦታ ሰጥታዋለች ማለት አይቻልም፡፡ በሆሣዕና ዕለት ቅዳሴው የሚጀመረው ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ነው፡፡ ቀዳሾች ሥጋ ወደሙን ከቤተልሔም ይዘው ወደመቅደስ የሚገቡት  እንደወትሮው በምሥራቁ በር ሳይሆን በወንዶች መግቢያ ነው፡፡ መዘምራን በቀኝና በግራ ሥጋ ወደሙ የያዙትን ቀዳሾቹን አጅበው እየዘመሩና ምንጣፍ እያነጠፉ ይገቡና ቅድስቱ ላይ ቆመው፣ በመዝሙረ ዳዊት “እናንት መኳንንቶች፥ በሮችን ክፈቱ፥ የዘላለም ደጆችም ይከፈቱ፥ የክብርም ንጉሥ ይግባ። ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው? እግዚአብሔር ነው፥ ብርቱና ኃያል፥ እግዚአብሔር ነው፥ በሰልፍ ኃያል።” (መዝ. 23፡7-8) የሚለውን ክፍል ዲያቆኑና ቄሱ ሕዝቡም እየተቀባበሉ ያዜማሉ።